ስለ እኛ

ታሪካችን

ስለ ቤተክርስቲያናችን

በሂውስተን በምህፃረ ቃል (CMSDSM) በመባል የሚታወቀው የደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በሂውስተን እና በአካባቢዋ ለሚኖሩ ክርስቲያኖች መንፈሳዊ አገልግሎት ለመስጠት ሐምሌ ፳፯ ቀን ፲፱፻፹፭ ዓ.ም. (Aug 4, 1993) የቅዱስ ሲኖዶስ ፈቃድ ተሰጥቶት ተመስርቷል።

በሂውስተን በፍትነት በማደግ ላይ ያለው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ማህበረሰብ፣ መጀመሪያ በቅዱስ ማርቆስ ግብፅ ቤተክርስቲያን መሰብሰብ የጀመረ ሲሆን፣ በኋላም በ፲፱፻፹፮ ዓ.ም. (December 1993) ፪.፭ ኤከር መሬት ገዝቶ እስከ ነሐሴ ፲፱፻፹፯ ዓ.ም. (August 1995) ድረስ በድንኳን ውስጥ አገልግሎት ሲሰጥ ቆይቷል።

በወቅቱ በምዕራብ ሲል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ይስሐቅ የአሁን ህንፃ መሰረት ድንጋይ ጣሉ። ቤተክርስቲያኑም ተገንብቶ ጥቅምት ፴ ቀን ፲፱፻፹፱ ዓ.ም. (November 9, 1996) በወቅቱ በአሜሪካ ነዋሪ በነበሩት በሦስቱም ሊቃነ ጳጳሳት (አቡነ ይስሐቅ፣ አቡነ ዜና ማርቆስ እና አቡነ መልክ ጼዴቅ) ተባርኮ ተመርቋል።

ይህ ንቁ ማህበረሰብ በሂውስተን እና በአካባቢው እየጨመረ የመጣውን ምእመን ለማስተናገድ እጅግ ትልቅ ህንፃ ለመገንባት ገንዘብ በማሰባሰብ ላይ ይገኛል።

ሙሉ ታሪኩን ያንብቡ →
፲፱፻፹፭ ተመሠረተ

የቤተክርስቲያን አባቶች

መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ብርሃኑ

መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ብርሃኑ

አስተዳዳሪ
መጋቤ ምስጢር ቀሲስ መኮንን

መጋቤ ምስጢር ቀሲስ መኮንን

የስብከተ ወንጌል ኃላፊ
ሊቀ ሥዩማን ቀሲስ ኃይሉ

ሊቀ ሥዩማን ቀሲስ ኃይሉ

ቄሰ ገበዝ
ቀሲስ ደረጀ

ቀሲስ ደረጀ

ካህን
ቀሲስ ክፍለ

ቀሲስ ክፍለ

ካህን